top of page
መተዳደርያ-ደንብ
በሀገራችን በኢትዮጵያ ከጥንት ጀምሮ እስከ አሁን እንደሚሰራበት የአንድ አካባቢ ነዋሪ ሕዝብ እርስበርሱ በማህበር(በዕድር) ተደራጅቶ በሞት ጊዜ ለቀብር ሲረዳዳ መቆየቱ ይታወሳል።እኛም በኮሎራዶ ስቴት በዴንቨር ከተማና አካባቢው የምንኖር ኢትዮጵያውያንና ትውልደ -ኢትዮጵያውያን ይህንኑ የሀገራችንን የመረዳዳት መልካም ባህል በመከተል : የማሀበሩ አባል ወይም ቤተሰብ ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ የቀብር ሥነ-ስርዓት ወጪን ለመሸፈን የሚረዳ ቀጥሎ በተመለከተው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት መረዳጃ ማህበር (ዕድር) አቋቁመናል።
መግቢያ፦
የማህበሩ አድራሻ በኮሎራዶ ስቴት በዴንቨር ከተማና አካባቢው ሲሆን ፤አድራሻው በኮሎራዶ የኢትዮጵያ ኮሙኒቲ ጽህፈት ቤት የሚገኝበት 1540 S Havana St Suite 308 Aurora, CO 80012 ቢሮ ቁጥር 308 ነው።
bottom of page